በሆሳዕና ከተማ የክረምት ወራት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል !!

የሆ//አስ//ኮሚኒኬሽን /ቤት ነሐሴ3/2014.

በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት /ቤት አማካኝነት እየተመራ የሚገኘው የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአሥራ አራት በተለዩ የስምሪት መስኮች ላይ እየተተገበረ እንደሚገኝ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ታደሰ ገልፀዋል

በተለይም በሄጦ ቀበሌ አስተዳደር በወጣቶች አደረጃጀት አማካኝነት በዓለሙ /ሃና /ቤት የክረምት ማጠናከርያ ትምህርት ለተማሪዎች በነፃ በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች አማካኝነት እየተሠጠ ያለዉ ተግባር መቀጠል ያለበት መሆኑንም ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ትምህርት /ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ዘመድኩን እና የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ / አበበ ሎላሞ በበኩላቸው ይህ ተግባር በቀጣይነት በሌሎች /ቤቶች ላይ በትኩረት የሚሰራ እና አስፈላጊዉም ትብብር እንደሚደረግላቸው በመግለፅ ለወጣቶቹ ያላቸዉን ምስጋና ገልጸዋል !!!

Share this Post