13
Oct
2022
የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጥቅምት 03/2015 ዓ.ም
በስልጠና ላይ የቀበሌው አመራር አካላት፣ የንግዱ ማህበረሰብ ፣የከተማው ጽ/ቤት የምጣኔ ጥናት የታስክ ትምህርትና ቅሬታ አጣሪ ዳይሬክተሮት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል ።
የቦቢቾ ቀበሌ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀጋዬ አለማየሁ እንደገለፁት መንግስት በፋይናንስ ምንጭነት ከሚጠቀምባቸው አንዱና ዋነኛው ግብር መሆኑን ጠቁመው ግብር ከነዋሪው ህብረተሰብ ተሰብስቦ ለራሱ ለህብረተሰቡ ለመሠረተ ልማቶች ሥራ የሚውል ጥሪት /ሀብት/ ከመሆኑ አንጻር የግብር ጉዳይ የግብር ሰብሳቢ ብቻ አለመሆኑን በመረዳት የመላ ህብረተሰብ ነዉ ስሉ ገልጸዋል ።
አክለውም ኃላፊው ግብር መክፈል እንደሚገባ ማመን ብቻ ሳይሆን ከስወራና ከማጭበርበር በፀዳ መልኩ ትክክለኛውን ገቢ በማሳወቅ በተደነገገው ጊዜ ውስጥ መክፈል እንዲችል ሁሉም ማህበረሰብ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል ።