18
Oct
2022
የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጥቅምት 08/2015 ዓ.ም
የአራዳ ቀበሌ አሰተዳደር ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አድነው ሰዴቦ እንደገለፁት መንግስት ግብር ከነዋሪው ህብረተሰብ ሰብስቦ ለራሱ ለህብረተሰቡ ለመሠረተ ልማቶች ሥራ እንደሚያውለው ግንዛቤ በመያዝ ሁሉም ዜጋ ለግብር አሰባሰብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ።
አክለውም በቀበሌው በ2014ዓ.ም ግብር አከፋፈል ወቅት የአራዳ ቀበሌ ግብር ከፋዮች የሚፈለግባቸውን የመንግስት ግብር በአምስት ቀናት ውስጥ ከፍለው በማጠናቀቅ ላሳዩት አርአያነት ያለው ተግባር በማመስገን በግብር ስወራ ዙሪያ የሚፈፅሙ ህገ-ወጥ ተግባራት በማጋለጥ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል ።