20
Oct
2022
ጥቅምት 10/2/2015ዓ.ም
የሆሳዕና አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ ደ/ር ደበበ ገብሬ ዛሬ እንደገለጹት የሆሳዕና ከተማና አካባቢው ህብረተሰብ የሚሳተፍበት የድጋፍ ሰልፍ በሠላም ለማጠናቀቅ ዝግጅት በማደረግ ላይ መሆኑን ጠቁመው በዕለቱ በከተማው የሚገኙ ተቋማትና የንግድ ድርጅቶች እስከ ጠዋቱ አራት ሰዓት የሰልፍ ስነ-ስርዓቱ እስኪጠናቀቅ ተቋሞቻቸውን ዘግተው የሰልፋ ተካፋዮች እንዲሆኑ አሳስበዋል ።
አክለውም በከተማው ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ መነሻውን ኮ/ል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ በማድረግ በአብዮ ኤርሳም ስቴድየም የሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ዋና ዓላማ ለአገራችን ሉአላዊነት መከበር አንደ ዜጋ የሚጠበቅብንን ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ከመንግስታችን ጎን መቆማችንን ለማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡