በሆሳዕና ከተማ የትራንስፖርት አገልገሎት የሚሰጡ አራት የባጃጅ ታክሲ ባለንብረቶች ማህበራት ዓመታዊ ጉባኤያቸውን ማካሄድ ጀመሩ ።

የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጥቅምት01/2015 ዓ.ም

የከተማው ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸው ጋዶሬ ዛሬ የሠላም የባጃጅ ታክሲ ባለንብረቶች ማህበር ጉባኤ በንግግር ሲከፍቱ እንደገለፁት ማህበራቱ በሚያካሄዱት ጉባኤ የ2014 ዓ.ም የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም እንዲሁም የኦዲት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ።

በተጨማሪም የ2015 ዓ.ም ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የሚደረግበት ሲሆን በቀጣይ ሦስት ተከታታይ ቀናት ብርሃን፣ፍቅርና አንድነት የባጃጅ ታክሲ ባለንብረቶች ማህበራት በተመሳሳይ ሁኔታ ጉባኤያቸውን እንደሚያካሂዱ ኃላፊው ጠቁመዋል ።

አክለውም በትራንስፖርት ዘርፍ ለትራፊክ አደጋ መንስኤ የሚሆኑ ችግሮች ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም አስረድተዋል ።

በመጨረሻም በህገ-ወጥ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪና ከታሪፍ በለይ በሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደምወሰድና የታለመለትን የነዳጅ ድጎማ ታጠቃሚ እንዲሆኑ ኃላፊው መልዕክት አስተላልፈዋል ።

Share this Post