የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አረጋዊነት የኢትዮጵያዊነት አሻራ የትውልድ አደራ ሁለተናዊ ክብር ለአረጋውያን በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የአረጋውያን ቀን በዓል አከበረ።

የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጥቅምት01/2015 ዓ.ም

አረጋውያንና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በዓሉ ሲከበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ31ኛ በሀገራችን ለ30ኛ ጊዜ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ለአረጋውያን የተደረጉ የድጋፍ ና እንክብካቤ ተግባራት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ቲርካሶ እንደገለጹት በከተማው ባለፋት ሦስት ወራት ለ1,543 አረጋዊውንና አቅመ ደካሞች ከ6 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል ።

የሆሳዕና ከተማ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ታደሰ በበኩላቸው የዓረጋውያን ቀን ስናከብር ለአረጋውያን ክብር በመስጠትና የሀገር ባለውለታ መሆናቸውን በመገንዘብ የሚደረግላቸውን ሁለተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል ።

 

 

 

 

 

Share this Post