በሆሳና ከተማ አሸባሪው ሕወሀት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ አባላት ላይ ክሕደት እና ጥቃት የፈፀመበት ሁለተኛ ዓመት መታሰቢያ <<መቼም አረሳውም>> በሚል መሪ ቃል የመንግስት ና የግል ተቋማት አመራሮች ፣ ሰራተኞች እና መላው ነዋሪ ባለበት ቦታ በመቆም የቀኝ እጁን በግራ ደረቱ ላይ በማድረግና ለሰማዕታቱ ያለውን ክብር በመግለጽ በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል ።

የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሊሬ ጀማል በከተማው በየካቲት 25/67 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በተካሄደው የአከባበር ሰነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት ዕለተ ሰኞ ጥቅምት 23/2013 ዓ.ም ለጥቅምት 24 አጥቢያ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ አባላት ሽበርተኛው ሕወሀት በክህደት ጥቃት መፈጸሙ ሁሌ የሚታወስና ፈፅሞ የማይዘነጋ ነው ።

አክለውም የዛሬውን የመታሰቢያ በዓል ኢትዮጵያ ባሸነፈችበትና የህወሐት አሸባሪ ሀይል በተሸነፈበት ማግስት የሚከበር በመሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም ከንቲባው ጠቁመዋል ።

የከተማው ት/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ዘመድኩን በበኩላቸው ህብረተሰቡ በተሠማራበት ሁሉ ውጤት በማስመዝገብ ሀገር ለመበተን ጥቃት የፈጸሙብንን ህወሀትንና ጀሌዎቹን በመመከት የሀገራችንን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ መስዋእት እየከፈለ ካለው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ጎን ደጀን በመሆን እያደረገ የለውን ድጋፍ በቀጣይነት ሊያረጋግጥ እንደሚገባም ተናግረዋል ።

በፕሮግራሙ ላይ የት/ቤቱ ተማሪዎች የመከላከያ ሠራዊታችን ጀግንነት የሚገልጹ ግጥሞችና ድራማዎች በማቅረቡ በዓሉን

አድምቀዋል።

"ጥቅምት 24ን መቼም አንረሳውም"!!!

Share this Post