በከሪደር ልማት አሁናዊ ሁኔታ እና በከተማው እየተሰሩ ባሉ የልማት ስራዎች ደስተኛ መሆናቸውን አንዳንድ የከተማው ነዋሪዎች ገለፁ።

የውሃ ፋውንተን የተሠራበት ቦታ ከዚህ ቀደም ቆሻሻ የሚጣልበት ቦታ ስለነበር ሰዎች ለተለያዩ ተላላፊና ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ስጠቁ የነበረ ቦታ መሆኑን ጠቅሰው አሁን ግን መንግስት ቦታውን ለተለያዩ ለልማት አገልግሎት በማዋሉ ለብዙዎች የማዝናኛ ቦታ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል ።

በዕለቱም በስራ ቦታ ያገኘው ምህረቱ መለሰ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ዋና ስራ አስካጅ አቶ ምህረቱ መለሰ በሰጡት አስተያየት ሴሌሜ የውሃ ፋውንቴን በውስጡ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ ሰናይ እሴቶችን በዉስጡ የያዘ መሆኑን ጠቅሰው የኮሪደር ልማት አጠቃላይ ስራዎችንም በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ እንደሆነም ተናግረዋል ።

በመጨረሻም የሆሳዕና ከተማ ምክትል ከቲባና የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታሪኩ ተከተልን ጨምሮ የዞንና የከተማ አመራሮችም ምልከታ አድርገዋል ።

በጌታቸው ደስታ

Share this Post