ኤስኦኤስ ህፃናት መንደር ሐዋሳ ሆሳዕና አራዳ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ በላይ ይልማ እንደአብራሩት በሆሳዕና ከተማ በአራዳ ቀበሌ ለሚገኙ 1000 ወላጅ አጥ ህፃናት ፣222 ለቤተሰቦች፣50 ወጣቶች፣ለብድር ተቋማትና ለ2 ትምህርት ቤቶች በ2015 ዓ.ም ላይ ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የተለያዩ የትምህርትና የቢሮ መጠነ ሰፊ ቁሳቁስ ድጋፍ ማበርከቱን ገልፀዋል ።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሊሬ ጀማል እን ኤስኦኤስ ህፃናት መንደር ሀዋሳ ሆሳዕና አራዳ የመንግስት ያልሆነ የግል ድርጅት አቅመ ደካሞችንና ወላጅ አጥ ህፃናትን በኢኮኖሚና በማህበራዊ እንድሁም በምግብ ራሳቸውን እንድችሉ ላበረከቱት ድጋፍ በማመስገን የቤተሰብና የልማት ፕሮጀክት በመቻቸላቸው መሠረት በመቆጠብ ከተረጂነት ተላቀው ረሳቸውን በመቻል ለሌሎች መረዳት የሚችሉበትን አቅም በመጎልበት ተጠናክሮ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል ።

ኤስኦኤስ ህፃናት መንደሮች ኢትዮጵያ የሀዋሳ ፕሮግራም ቢሮ የዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ደጃኔ በበኩላቸው ፕሮጄክቱ ከ42 ሚልዮን ብር በላይ በጀት ተበጅቶለት መጠነ ሰፊ ሥራዎችን በመስራት ላይ የሚገኝ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል ።

አክለውም የቤተሰብ እና የልማት ድርጅቱ

በህፃናት ላይ ትኩረት በማድረግ የወላጅን እንክብካቤ ለጡትና የወላጅን እንክብካቤ እንዳያጡ የመከላከል ሥራን በህብረተሰቡ ላይ በማጽረጽ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ

የቆየው ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰዋል ።

አንዳንድ አስተያየት የሰጡት ኤስኦኤስ ህፃናት መንደር ሐዋሳ ሆሳዕና አራዳ ፕሮጀክት ልጆቻቸውን የማማሪን ዕድል ያገኙበትና ለሁለት ትምህርት ቤቶች እንድሁም ለተለያዩ ተቋማት የተለያዩ የቢሮና የትምህርት ቁሳቁስ ላበረከቱት ድጋፍ አመስግነዋል ።

Share this Post