የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ም/ ከንቲባ አቶ በየነ ሸንቆ የ2015 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ም/ ከንቲባ አቶ በየነ ሸንቆ የ2015 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጰጉሜ 04/2014 ዓ.ም

አቶ በየነ ሸንቆ በመልዕክታቸው የከተማችን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዓሉን ሲያከብሩ የዘማች ቤተሰቦች ፣ አቅመ ደካሞችና በጦርነቱ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በመርዳት መሆን እንዳለበትም ጠቅሰዋል ።

የከተማችን ነዋሪዎች የሀገራችን ሉአላዊነትን ለማስከበር የህይወት መስዋት ለሚከፍለው መከላከያ ሠራዊት ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ በማመስገን ድጋፋቸውን በሌሎች የልማት ሥራዎች አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል ።

አክለውም ህብረተሰቡ የእርድ እንስሳት ተረፈ ምርቶች በተገቢው በማስወገድ የአካባቢውን ንፅህና ሊጠብቅ እንደሚገባም በመልዕክታቸው ጠቁመዋል ።

Share this Post