የሆሳዕና ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 9ኛ የሥራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ እንደ ቀጠለ ነው።

የሆሳዕና ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 9ኛ የሥራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ እንደ ቀጠለ ነው።

ሆሳዕና ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን ገዳዮች ጽ/ቤት ነሐሴ 5/2014 ዓ.ም

የምክር ቤቱ ጉባኤ በትላንትናው ዕለት የ21ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ ፣የም/ቤቱ ጽ/ቤት የ2014 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀና የ2015 ዓ,ም ጠቋሚ ዕቅድ ገምግሞ ያፀደቀ ሲሆን የከተማው አስተዳደር የ2014 ዓ.ም ማጠቃለያ የክንው ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።

የምክር ቤቱ አባላት በዛሬው ዕለት የአስፈፃሚውን አካል መነሻ በማድረግ በከተማው በመሬት አስተዳደር ፣ በአገልግሎት አሠጣጥ ፣ በገቢ አሰባሰብ ፣ በመሠረተ -ልማት ፣ በትምህርት ጥራት ፣ በህገ-ወጥ ንግድ ፣ በትራንስፖርትና በሌሎች ዘርፎች የሚታዩ ችግሮች እንዲፈቱ ላቀረቡዋቸው ጥያቄዎች በም/ከንቲባ በአቶ በየነ ሻንቆና በሚመለከታቸው የካቤኔ አካላት ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቷል ።

የም/ቤቱ አባላት በሌሎች አጀንዳዎች ላይ ውይይታቸውን ቀጥለዋል ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን 2ኛ ተርባይን ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ እንኳን ደስ አላችሁ ፤እንኳን ደስ አለን !!

Share this Post