የሃዲያ ሆሳዕና ተጨዋቾች ከደጋፊዎች ጋር ትውውቅ አደረጉ

የሃዲያ ሆሳዕና ተጨዋቾች ከደጋፊዎች ጋር ትውውቅ አደረጉ

የሃዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ ተጨዋቾችና አመራሮች ከደጋፊዎች ጋር ትውውቅ አደረጉ።

የሃዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ ለ2015 ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ብርቱ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቅረብ የተለያዩ ተጨዋቾችን በማስፈረም ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል።

በዛሬው ዕለት ተጨዋቾችንና አመራሮችን ከደጋፊው ጋር አስተዋውቋል።

በትውውቅ ፕሮግራም ላይ በርካታ ደጋፊዎች የተገኙ ሲሆን እንዲሁም የሃዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እንዲሁ የክለቡ የበላይ ጠባቂ አብርሃም መጫና የሃዲያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የክለቡ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ_ፀጋዬ ተገኝተዋል።

ምንጭ:-ሆሳዕና ስፖርት

Share this Post